በቀን በቀን 13 -07 -2017 ዓ.ምየጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በባለፉት 8 ወራት ከአጎራባች ኦሮሚያ ሸገር ከተሞች የመነ አብቹ እና ኤጀርሳ ጎሮ ጋር በቅንጅት በተከናወኑ ተግባራት የህብረተሰቡን ሰላምና ጸጥታ ማስጠበቅ መቻሉን ተገለጸ።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ መነ አብቹ እና ኤጀርሳ ጎሮ ጋር ባለፉት ስምንት ወራት በቅንጅት የተሰሩ የሰላምና ጸጥታ ስራዎችና በቀጣይ በሚከተናወኑ ተግባራት ዙሪያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ።
ጽ/ቤቱ በባለፉት 8 ወራት ከአጎራባች የሸገር ከተሞች ጋር በጋራ በመሆን ህገ ወጥነትን በመከላከል ፣ በሰላም ጉዳይ የህዝብ ለህዝብ ትስስር በመፍጠር ፣ ጠንካራ የመረጃ ቅብብሎሽ ስርዓት በመፍጠር የተለያዩ የጽንፈኛ ሃይሎች እንቅስቃሴ በማክሸፍ ፣ የጸጥታ የጋራ ግብረ ሃይል የህግ ማስከበር ስራዎች ፣ የፍተሻና የአሰሳ ስራዎች በማከናወን ሃይማኖታዊና የአደባባይ በዓላትና የተለያዩ ሁነቶችን ያለምንም የጸጥታ ችግር ማክበር መቻሉን ተገልጿል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ እንደተናገሩት በባለፉት 8 ወራት በቅንጅት በትብብር በመስራት በተከናወኑ ተግባራት በወንጀል ቅነሳ ፣ የጽንፈኛ ሃይሎች እንቅስቃሴ ቀንሷል ያሉ ሲሆን በቀጣይ የኢኮኖሚ አሻጥር ለመከላከል ፣የመጋዘን ፍተሻ የነዳጅ ፣ የገቢ ስወራ በመከላከል ረገድም ትልቅ ለውጥ መምጣት መቻሉን ገልጸዋል።