Loading...

ዋና ዋና ዜናዎች

ዋና ዋና ዜናዎች

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ብሎሞ በከተማው የተከናወኑ ክንውኖች

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት መሪ እቅድን ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በ2017 በጀት አመት አስተዳደሩ የሰላምና ጸጥታ ጉዳይን ከክፍለ ከተማው ነዋሪዎች እንዲሁም ከጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅቶ ውጤታማ ስራ መስራቱን በመግለፅ ባለፈው በጀት አመት የነበሩ ክፍተቶችን በጋራ ለይቶ በማረም በቀጣይ ለተሻለ አፈፃፀም ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል ።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ እንደተናገሩት ለክፍለ ከተማችን ሰላም መጠበቅ በተለይ የሰላም ሰራዊቱ የነበራቸውን ሚና አመስግነው በቀጣይም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለአከባቢው ሰላም መጠበቅ ባለቤት ሆኖ በቅንጅት መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በመድረኩ የ2017በጀት ዓመት የተቋሙ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 መሪ እቅድ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በሰላም እሴት ግንባታ ፣ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ እና በማደራጀት የአካባቢውን እንዲጠብቅ በማድረግ በዓላት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቁ ማድረግ ፣የወንጀል ድርጊቶችን መለየት እና መከላከል በቅንጅት ተባብሮ በመስራት የነዋሪውን ደህንነት በተሻለ መልኩ ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እንደተሰራ ተብራርቷል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የ2017 በጀት አመት አፈፃፀም ውጤታማ ስራዎች የተሰሩበት እንደነበር በማንሳት በሰላም ጉዳይ ላይ ሁሉም ባለቤት ሆኖ በመሳተፍ የበኩላቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም አስተዋፅኦ ላበረከቱ ለክፍለ ከተማ ሴክተር ተቋማት ፣ የፌዴራልና የከተማ ፖሊስ መምሪያ አባላት ፣ ለሰላም ሰራዊት ፣ለወረዳዎች የምስክር ወረቀትና የዋንጫ ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር የጸጥታ ጥምር ሃይል መጪውን የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቅ በተሰሩ የሰላምና ጸጥታ ማስጠበቅ ስራዎችና በቀጣይ የክፍለ ከተማውን የጸጥታ ሁኔታ በተጠናከረ አሰራር ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ውይይት አድርጓል።

ውይይቱን የመሩት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩት በዓላት በሰላም እንዲከበሩ የጸጥታ ጥምር ሃይሉ መጪውን የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት ሰላማዊ ሆነው እንዲከበሩ ለማድረግ ቅንጅታዊ ስራዎችን ለቀጣይ አጠናክሮ በመሰራትና የነበሩ ክፍተቶችን በማረምና በማስተካከል የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ በትኩረት መንቀሳቀስ ይገባል ብለዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ በበኩላቸው በክፍለ ከተማ ደረጃ በተሰራው የተቀናጀ ስራ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውንና ለጸጥታ ስጋት የተባሉትን ከአጎራባች የኦሮሚያ ከተሞች ጋር በመቀናጀት ፍተሻና አሰሳ ስራዎች ተጠናክረው በመሰራት ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አራጌ እሸቴ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከር ለማድረግ የጸጥታ መዋቅሩ ከሰላም ሰራዊቱ ጋር በመናበብ የስምሪትና የመረጃ ልውውጥ ስርዓታችንን በማስተካከል ህብረተሰቡ ሰላሙን ከጸረ ሰላም ሃይሎች እንዲጠብቅ በማድረግ በዓሉ በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ ማስቻል ይገባል ብለዋል።

በቀጣይ የፀጥታ ኮማንድ ፖስቱ የሰላም ሰራዊቱን ማጠናከር፣ ስጋት ያለባቸው ቦታዎችን የተለየ ፣ ሁለቱን የአደባባይ በዓሎች በቅንጅት በመስራት ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር የጸጥታ ጥምር ሃይል መጪውን የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ በተሰሩ የሰላምና ጸጥታ ማስጠበቅ ስራዎችና በቀጣይ የክፍለ ከተማውን የጸጥታ ሁኔታ በተጠናከረ አሰራር ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ውይይት አድርጓል።

ውይይቱን የመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ፣ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ ኢሬቻ በዓል በህብርብሔራዊ አንድነት ፣ በፍቅር ፣በሰላም በዪኒስኮ የተመዘገበ በመሆኑ ገቢ የሚያመንጩ አደባባይ በዓል ሰለሆኑ ባህላዊ ትውፊቱን ጠብቆ ከዚህ በፊት እንደምናከብራቸው አደባባይ በዓላት ያለምንም አንዳች ችግር ከብሎክ አመራሮችና ከጸጥታ አካለት ጋር በመቀናጀት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በበኩላቸው በክፍለ ከተማ ደረጃ በተሰራው የተቀናጀ ስራ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውንና ለጸጥታ ስጋት የተባሉትን ነገሮች ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ከአጎራባች የኦሮሚያ ከተሞች ጋር በመቀናጀት ፍተሻና አሰሳ ስራዎች ተጠናክረው በመሰራት ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድር በከተማዋ የኢሬቻ በዓል ባህላዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከር ለማድረግ የጸጥታ መዋቅሩ ከሰላም ሰራዊቱ ጋር በመናበብ የስምሪትና የመረጃ ልውውጥ ስርዓታችንን በማስተካከል ህብረተሰቡ ሰላሙን ከጸረ ሰላም ሃይሎች እንዲጠብቅ በማድረግ በዓሉ በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ ማስቻል ይገባል ብለዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አቶ ሀብታሙ ደረጀ በበኩላቸው በዓሉ በሰላም እንዲከበር የጸጥታ ጥምር ሃይሉ ቅንጅታዊ ስራዎችን ለቀጣይ አጠናክሮ በመሰራትና የነበሩ ክፍተቶችን በማረምና በማስተካከል የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ በትኩረት መንቀሳቀስ ይገባል ብለዋል።

በቀጣይ የፀጥታ ኮማንድ ፖስቱ የሰላም ሰራዊቱን ማጠናከር፣ ስጋት ያለባቸው ቦታዎችን የተለየ ፣ በዓሉን በቅን

በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የአዲሱ ገበያ የአንድ ማዕከል የሰላም ሰራዊት ስምሪት የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ፣ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ ፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚና ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰ ፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ጎዴቦ ፣ የከተማ ደጋፊ አመራሮች ፣ የፖሊስ አመራሮች ሌሎች የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት የአንድ ማዕከል ህዝባዊ የሰላም ሰራዊት ስምሪት ተሰጠ።

በመርሃ ግብሩ ላይ ስምሪት የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ፣ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ በመልዕክታቸው የሰላም ሰራዊቱ ከፀጥታ ሀይሉና ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት የአከባቢውን ሰላምና ደህንነት በንቃት እየጠበቀ ያለበት ሁኔታ አበረታች መሆኑን ገልፀው ስምሪት ወስዶ አከባቢን መጠበቅ የሰላም ሰራዊት የዘወትር ተግባር በመሆኑ በበዓላት ወቅት በልዩ ትኩረት አከባቢን የመጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚና ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰ በበኩላቸው ሀይማኖታዊ እና ህዝባዊ የአደባባይ በዓላት በሚከበርበት ወቅት የህብረተሰቡን ሰላም ለማደፍረስ አጋጣሚውን የሚጠቀሙ ሀይሎች በመኖራቸው ህዝባዊ የሰላም ሰራዊቱ አካባቢውን የፀጥታ ችግሮች እንዳይከሰቱ መስራት ይገባል ብለዋል።

አቶ ሰለሞን አክለውም ህዝባዊ የሰላም ሰራዊት አባላትም የአካባቢያቸውን ሰላምና ፀጥታ አንዳች ችግር እንዳይከሰት ማንኛውንም ችግሮች ተጋፍጠው ስምሪታቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸው በየደረጃው ያሉ የወረዳው የፓሊስ ሰራዊት አባላት፣የሰላም ሰራዊት ፣የቅጥር ጥበቃ እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች የምስጋና እና የማበረታቻ መልእክት አስተላልፈዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አራጌ እሸቴ በበኩላቸው የመስቀል ደመራ እና ኢሬቻ በዓላት በሚከበርበት ወቅት በርካታ ህዝብ የሚሰባሰብባቸው እንደመሆኑ መጠን በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ ከብሎክ ጀምሮ የምንሰራው የፀጥታ ስራ እጅግ ወሳኝነት አለው የአንድ ማዕከል ህዝባዊ የሰላም ሰራዊት ስምሪት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ገልፀው ከማመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር ተናቦ መስራት እንደሚገባም ገልፀዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ፓስተር ፖሊስ ጣቢያ የቢሮ ግንባታ አጠናቆ አስመረቀ።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ፓስተር ፖሊስ ጣቢያ የክፍለ ከተማ አመራሮች የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ አዛዦች የጣቢያ አመራሮች በተገኙበት አስመርርቋል።

በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ እንደተናገሩት የክፍለ ከተማውን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ከሌሎች አጋር የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ቀንና ሌሊት ከአስተዳደሩ ጋር በመስራት በርካታ ሁነቶች ያለምንም ኮሽታ ማክበር መቻሉን ተናግረው ፖሊስ ተቋማዊ ሁኔታዎች በማረጋገጥ በዛሬው ዕለት የተመረቀው የፓስተር ፖሊስ ጣቢያ ምርቃት ለምንሰጠው የሰላምና ጸጥታ ተግባር አስተዋጽዖ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አራጌ እሸቴ በበኩላቸው ፖሊስ መምሪያው ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የማይተካ ሚና በመጫወት ህብረተሰቡ ሰላም ወጥቶ መግባቱን እንዲያረጋግጥ ወንጀሎች ሳይፈጸሙ በመከላከልና በመቆጣጠር በርካታ ተግባራት ያከናወነ መሆኑን በመግለጽ በወረዳ 9 ፓስተር ፖሊስ ጣቢያ ምርቃት የፀጥታ ኃይሉ የጀመረውን ቁጥጥርና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል ሚናው የጎላ ነው በመሆኑም ይህንን ግንባታ ለደገፉና ላስተባበሩ ተቋማት በፖሊስ መምሪያ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ኃላፊው አክለው መላው የፀጥታ አካላት አመራሮችና አባላት እንደከዚህ ቀደሙ የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት በሳላም እንዲከበሩ ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡም የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

ለጣቢያው ግንባታ የላቀ አስተዋጽዖ ላበረከቱ የተለያዩ አካላት የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

በስነ ስርዓቱ ላይ የክፍለ ከተማ አመራሮች የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ አዛዦች የጣቢያ አዛዦች እንዲሁም የፖሊስ አባላት ተገኝተዋል።

የሰላም ሰራዊቱ ከፊታችን ቀናት በድምቀት የሚከበሩ የአደባባይ በዓላት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከበሩ የአካባቢውን ሰላምና ጸጥታ ማስጠበቅ እንዳለበት ተገለጸ።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት " በእምርታና ማንሰራራት የታጀበ ሀይማኖታዊና ህዝባዊ በዓላት ያለምንም የጸጥታ ችግር መከበር የሰላም ሰራዊቱ ሚና " በሚልመሪ ሃሳብ በቀጣይ በሚከበሩ የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓል እንዲከበር ዙሪያ ከ10ሩም ወረዳ ከተውጣጡ የሰላም ሰራዊት አባላት ት ጋር የፓናል ውይይት አካሂዶል ፡፡

በውይይቱ ላይ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ እንደገለጹት የመስቀልና ኢሬቻ በዓል በህብርብሔራዊ አንድነት ፣ በፍቅር ፣በሰላም በዪኒስኮ የተመዘገቡ በመሆናቸው ገቢ የሚያመንጩ አደባባይ በዓል ሰለሆኑ ሀይማኖታዊ እሴቱንና ባህላዊ ቱፊቱን ጠብቆ መከበር እንዳለበት ገልጸው ለዚህም የሰላም ሰራዊቱ ሚና የጎላ በመሆኑ ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴታቸውን ጠብቀው በሰላም እንዲከበሩ አካባቢውን መጠበቅ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል ፡፡

የውይይቱ ተሳታፊ የሰላም ሰራዊት አባላት የሰላም ሰራዊት አባሎቻችን የመስቀልና ኢሬቻ በዓልን ልክ ከዚህ በፊት እንደምናከብራቸው አደባባይ በዓላት ያለምንም አንዳች ችግር ከብሎክ አመራሮችና ከጸጥታ አካለት ጋር በመቀናጀት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

" የሰላም ሰራዊቱ የከተማዋን ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ እያከናወነ ለሚገኘውን ተግባር የከተማው አስተዳደር ምስጋናው የላቀ ነው። " ፦ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ

በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሽሮሜዳ ክላስተር በመገኘት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ፣ ፣የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶችና ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ ፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ የከተማ ደጋፊዎች ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች የአንድ ማዕከል ስምሪት ላይ በመገኘት የሰላም ሰራዊቱን አበረታተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት የሰላም ሰራዊቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በከተማችን ላይ የተካሄዱ ሃይማኖታዊ ፣ ህዝባዊና የአደባባይ በዓላቶች የተለያዩ አለም አቀፍ ስብሰባዎች ያለምንም ጸጥታ ችግር ተካሄደው እንዲጠናቀቁ ከሌሎች የጸጥታ መዋቅር ጋር በመሆን የአንበሳውን ድርሻ ተወጥቷል ያሉ ሲሆን በቀጣይ ቀናት የሚከበሩትን የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቁ ለማስቻል የስምሪት አግባባችሁን በማጠናከርና የጸጉረ ልውጥ እንቅስቃሴዎችን በማጋለጥ ከሌሎች ጸጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀት የአርበኝነት ሚናችሁን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው ሰላምና ጸጥታ እንዲረጋገጥ የሰላም ሰራዊቱ የላቀ ድርሻውን እያበረከተ ይገኛል ያሉ ሲሆን ከፊታችን የሚከበሩ ሃይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት ስርዓታቸውን ጠብቀው ያለ ምንም የጸጥታ ችግር እንዲከበሩ የሰላም ሰራዊቱ የአካባቢውን ሰላም ከጸረ ሰላም ሃይሎች በመጠበቅ እንዲከበር መስራት አለበት ብለዋል።

የሃይማኖት አባቶች የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት ፍጹም ሰላማዊ ሆነው እንዲከበሩ ከመንግስት በቅንጅት እንደሚሰሩ ገለጹ።

(ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣10 -01 -2018 ዓ.ም)

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት በቀጣይ ሳምንታት የሚከበሩ የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላትን ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲከበሩ ከሃይማኖት አባቶች ፣ ከሰበካ ጉባዔ አባላት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋር ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ እንደተናገሩት የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት በአደባባይ ህዝብ ወጥቶ የሚያከብራቸዉና ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የሚተላለፉ ሃማኖታዊና ባህላዊ በዓላት ወግና ትዉፊታቸዉን ሳይለቁ እንዲከበሩ የሃይማኖት አባቶች ተከታዮቻቸውን ግንዛቤ እንዲያገኙ የሰላምን አስፈላጊነት በአስተምህሮቶ ቻቸው ውስጥ በሰፊው በማዳረስ ኃላፊነታችሁን መወጣት ይገባል ብለዋል።

የሃገራችን የዘመናት የባህልና እሴት የአንድነት ተምሳሌት የሆኑ የአደባበይ በዓሎችን ለማክበር የእምነት አባቶች ሚና የላቀ በመሆኑ በዓላቶቻችን የመከባበርና የመተባበር ተምሳሌቶቻችን እንደሆኑ ሁላችንም በየቤተ እምነቶቻችን ለተከታዮቻችን በማስገንዘብ ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች ሃገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መጋቢ ሥርዓት የቻለው ለማ በበኩላቸው ሁለቱም በዓለት ሲከበሩ አንዳንድ እኩይ ተግባር እና የፀጥታ ችግር ሊፈጥሩ የሚችሉ አከላትን የቤተ እምነት አባቶች ከሁሉም የፀጥታ አከላት ከፌደራል ፖሊስ፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ እና ከሰላም ሰራዊት ጋር በቅንጀት በመንቀሳቀስ ሴራቸዉን ማክሸፍ ይገባል ብለዋል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸዉ የመስቀል ደመራ እና ኢሬቻ በዓላት ለኢትዮጵያ የመቻቻል ፣የአንድነት እሴት የሚያጎለብቱ እንዲሁም አብሮ የመኖር ተምሳሌት በመሆናቸዉ በዓሉ ያለምንም ፀጥታ ችግር እንዲከበር ከመንግስት ጋር በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል ፡፡

#ጳጉሜ_1_የጽናት_ቀን

በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጷጉሜ 1 የጽናት ቀንን ምክንያት በማድረግ "ፅኑ መሰረት ብርቱ ሀገር" በሚል መሪ ቃል የመስዋዕትነት አርማ የሆነውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ሰነ ስርዓት በድምቀት ተከናውኗል።

በስነ- ስርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩት ጳጉሜ 1 የፅናት ቀንን ስናከብር ሀገራችን ኢትዮጵያ የተለያዩ ተግዳሮቶችን በማለፍ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ስኬታማ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን በመገንዘብ መሆን አለበት ያሉ ሲሆን ሀገራችን የጀመረቸውን የለውጥ ጉዞ ለማሳለጥ ጀግንነት እና በጽናት ለሀገር እድገት እና ብልጽግና በጋራ መቆም ይገባናል ብለዋል፡፡

የዛሬው ዕለት የጀግንነት ፣የጽናት የአንድነት ተምሳሌት የሆኑ ጀግኖችን በሚተጉ ክብር የሚሰጥበት ለሀገራችን ለውጥ በጋራ የምንተጋበት ነው ብለዋል ።

በስነ ስርዓቱ ላይ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች የፌደራልና የከተማ ፖሊስ አባላት ፣ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የሰላም ሰራዊት አባላት እንዲሁም ሴቶችና ወጣቶች በተገኙበት ተከናውኗል።

#ጳጉሜ_1_የጽናት_ቀን

ትውልዱ በሃገራዊ ጥቅም ላይ ባለመደራደር ጽኑና ሃያል የሆነች ኢትዮጵያን መገንባት እንደሚገባ ተገለጸ።

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ጳጉሜን አንድ የጽናት ቀን "ፅኑ መሠረት ብርቱ ሀገር" በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት አካሄደ።

በፓናል ውይይቱ ላይ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩትን ሃገራችን ኢትዮጵያ በበርካታ ፈተናዎችን በማለፍ በጽናት ያከናወናቸው የአረንጓዴ አሻራ ተግባራችን ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ፣ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶቻችን እንደ ሀገር ያለንን አይበገሬነት እና በፈተና ሳንበገር ወደ ፊት መጓዝ ስለ መቻላችን ማሳያ ነው ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው አክለውም የጽናት ቀንም ፈተናዎችን በፅናት በማለፍ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማስመዝገብ እየተደረጉ የሚገኙ ብርቱ ጥረቶችን በመዘከር ለአዳዲስ ተልዕኮዎች እና ለላቁ ድሎች የምንዘጋጅበት ነው ብለዋል፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ የሀገር ወዳድነት ፣ የፅናትና የአርበኝነት ምንነቶችን በሰፊው የሚዳስስ የማወያያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የጸጥታና የደኅንነት ተቋማትን ከማዘመን ጀምሮ እስከ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እውን መሆን ድረስ ያገኘነው ታላቅ ስኬት፤ የአንድነታችን፣ የጋራ ዓላማችን እና ያላሰለሰ ጽናታችን ውጤት መሆኑን በኩራት እናረጋግጣለን ለእነዚህ ስኬቶች መንገድ የከፈቱት ጀግኖቻንን ድፍረት፣ የመስዋዕትነትና የማይናወጥ ጽናትን እናስታውሳለን፤ እናከብራለንም ብለዋል።

የዛሬው ዕለት ፈተናዎችን ሁሉ ወደ መልካም አጋጣሚ ቀይረን ኢትዮጵያን ወደ አዲስ የብልጽግና፣ የክብርና የዘላቂ ከፍታ ለማድረስ ቃል የምንገባበት ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በአዲስ ተስፋ፤ በጽኑ መንፈስና በማይናወጥ አንድነት መቆም እንደሚገባ አስረድተው፤ ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግናና ታላቅነት የምታደርገውን ጉዞ በይበልጥ ከፍ የምታደርግበት አዲስ ምዕራፍ መጀመሩንም ገልጸዋል።

በፓናል ውይይት ላይ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች የፌደራልና የከተማ ፖሊስ አባላት ፣ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የሰላም ሰራዊት አባላት እንዲሁም ሴቶችና ወጣቶች ተሳትፈዋል ።

#ጳጉሜ_1_የጽናት_ቀን

ትውልዱ በሃገራዊ ጥቅም ላይ ባለመደራደር ጽኑና ሃያል የሆነች ኢትዮጵያን መገንባት እንደሚገባ ተገለጸ።

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ጳጉሜን አንድ የጽናት ቀን "ፅኑ መሠረት ብርቱ ሀገር" በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት አካሄደ።

በፓናል ውይይቱ ላይ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩትን ሃገራችን ኢትዮጵያ በበርካታ ፈተናዎችን በማለፍ በጽናት ያከናወናቸው የአረንጓዴ አሻራ ተግባራችን ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ፣ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶቻችን እንደ ሀገር ያለንን አይበገሬነት እና በፈተና ሳንበገር ወደ ፊት መጓዝ ስለ መቻላችን ማሳያ ነው ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው አክለውም የጽናት ቀንም ፈተናዎችን በፅናት በማለፍ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማስመዝገብ እየተደረጉ የሚገኙ ብርቱ ጥረቶችን በመዘከር ለአዳዲስ ተልዕኮዎች እና ለላቁ ድሎች የምንዘጋጅበት ነው ብለዋል፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ የሀገር ወዳድነት ፣ የፅናትና የአርበኝነት ምንነቶችን በሰፊው የሚዳስስ የማወያያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የጸጥታና የደኅንነት ተቋማትን ከማዘመን ጀምሮ እስከ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እውን መሆን ድረስ ያገኘነው ታላቅ ስኬት፤ የአንድነታችን፣ የጋራ ዓላማችን እና ያላሰለሰ ጽናታችን ውጤት መሆኑን በኩራት እናረጋግጣለን ለእነዚህ ስኬቶች መንገድ የከፈቱት ጀግኖቻንን ድፍረት፣ የመስዋዕትነትና የማይናወጥ ጽናትን እናስታውሳለን፤ እናከብራለንም ብለዋል።

የዛሬው ዕለት ፈተናዎችን ሁሉ ወደ መልካም አጋጣሚ ቀይረን ኢትዮጵያን ወደ አዲስ የብልጽግና፣ የክብርና የዘላቂ ከፍታ ለማድረስ ቃል የምንገባበት ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በአዲስ ተስፋ፤ በጽኑ መንፈስና በማይናወጥ አንድነት መቆም እንደሚገባ አስረድተው፤ ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግናና ታላቅነት የምታደርገውን ጉዞ በይበልጥ ከፍ የምታደርግበት አዲስ ምዕራፍ መጀመሩንም ገልጸዋል።

በፓናል ውይይት ላይ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች የፌደራልና የከተማ ፖሊስ አባላት ፣ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የሰላም ሰራዊት አባላት እንዲሁም ሴቶችና ወጣቶች ተሳትፈዋል ።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በ2018 በጀት ዓመት ሃይማኖታዊ እና የአደባባይ ክብረ በዓላት በሰላም እንዲጠናቀቅ ላደረጉ የሰላም ሰራዊት እና የጸጥታ አባላት የምስጋናና ፣ የዕውቅና ፕሮግራም አካሄደ።

በምስጋና እና በዕውቅና መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት የሰላም ሰራዊቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በከተማችን ላይ የተካሄዱ ሃይማኖታዊ ፣ ህዝባዊና የአደባባይ በዓላቶች የተለያዩ አለም አቀፍ ስብሰባዎች ያለምንም ጸጥታ ችግር ተካሄደው እንዲጠናቀቁ ከሌሎች የጸጥታ መዋቅር ጋር በመሆን የአንበሳውን ድርሻ ተወጥቷል ያሉ ሲሆን በቀጣይ የስምሪት አግባባችሁን በማጠናከርና የጸጉረ ልውጥ እንቅስቃሴዎችን በማጋለጥ ከሌሎች ጸጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀት የአርበኝነት ሚናችሁን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩት ሃይማኖታዊና ባህላዊ በዓላቶቻችን በክፍለ ከተማችን በሰላማዊ መንገድ እንዲከበሩና እንዲጠናቀቁ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ልዩ ትኩረት በመስጠት በቅንጅት በመንቀሳቀሳችን ውጤት መምጣቱ ገልጸው ለሁሉም በክፍለ ከተማው አስተዳደር ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው አክለውም ይህንን የቅንጅት ተግባር በቀጣይ በተለያዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች በህብረተሰቡ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ በመተግበር የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታት መስራት ይገባል ብለዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ በበኩላቸው በክፍለ ከተማችን ሃይማኖታዊና ባህላዊ የአደባባይ በዓላት ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ጠንካራ የአመራር ስምሪት በመስጠት ለህብረተሰቡ ሰፊ ግንዛቤ በማስያዝ ከጸጥታ አካላትና ከአጎራባች የኦሮሚያ አጎራባች ከተሞች እንዲሁም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በጋራ በመስራት ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ተሰርቷል ብለዋል።

በምስጋና እና በዕውቅና መርሃ ግብሩ ላይ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ፣የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ፣ የሰላም ሰራዊት አመራሮችና አባላት ፣ ነዋሪዎች ተሳትፈውበታል።

በክፍለ ከተማው ሰላምና ጸጥታ በማስጠበቅ አስተዋጽዖ ላበረከቱ ለክፍለ ከተማ ሴክተር መስሪያ ቤቶችና ለ10ሩም ወረዳዎችና ፣ ለሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ፣ ለፌደራል እና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ፣ ለሸገር ከተማ አስተዳደር ለሰላም ሰራዊት አባላት የዋንጫና ዕውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት ክፍለ ከተማ አቀፍ የፖሊስ ሰራዊት ስፖርታዊ ውድድር ተጠናቀቀ ።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የፖሊስ ሰራዊት የእጅ ኳስ የስፖርታዊ ውድድር አካሄዷል ::

በመዝጊያ ስነ ስርዓቱ ላይ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት አቶ ሀብታሙ ደረጀ እንደተናገሩት የጸጥታ አካላት ከሚያከናውኑት መደበኛ ወንጀልን ከመከላከልና የጸጥታ ስራዎችን ከማከናወን ባሻገር ጤንነቱን የተጠበቀ በአካላዊ ብቃት የዳበረ አስተማማኝ ግዳጅ በአግባቡ የሚወጣ የፖሊስ ሰራዊት ለመፍጠር የስፖርቱን ዘርፉ ማጠንከር ይገባል ያሉ ሲሆን የሰራዊት የስፖርት ውድድር እህትማማችነት ወንድማማችነት ያጠነክራል ለተወዳደሪዎች መልካም ዕድልን ተመኝተዋል ::

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ሞቱማ ሰማ በበኩላቸው የፖሊስ ሰራዊት ከሰላም ማስከበር በተጨማሪ በስፖርታዊ ውድድር ትውውቅን በመፍጠር አብሮነትን ለማሳደግ ይጠቅማል ብለዋል።

የማጠቃለያ ስፖርታዊ ውድድሩ ማጠቃለያ በመረብ ኳስ የተካሄደ ሲሆን ፓስተር ፖሊስ ጣቢያ የጉለሌ ፖሊስ መምሪያ አሸናፊ ሆኗል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከክፍለ ከተማው ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር ያስገነባቸውን 2 የአቅመ ደካማ ቤቶችን አስመረቀ።

በምርቃት መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እንደተናገሩት በሰው ተኮር ስራዎች መንግስት የአቅመ ደካማ ቤቶችን በማደስ አብሮነትን መረዳዳትን ባህል ለማድረግ በትኩረት እየሰራ እንደሆነ በመግለጽ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ በርካታ የበጎ ፈቃድ ተግባራት በማከናወን በመረዳዳትና በመተጋገዝ ድህነትን እናሸንፋለን ያሉ ሲሆን አቅመ ደካሞችን ችግር በመረዳት ድጋፍ የሚያደርጉ ተቋማትና የግል ባለሀብቶች ሊመሰገኑ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ደረጀ በበኩላቸው ጽ/ቤቱ በመደበኛነት የህብረተሰቡን ሰላምና ጸጥታ ከማስጠበቅ ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በክረምት በጎ ፈቃድ ለ11 አቅመ ደካማ ወገኖች የቤት ዕድሳት ማድረጉን ገልጸው ከዚህ ውስጥ በዛሬው ዕለት 2 የአቅመ ደካማ ቤቶችን ማስመረቅ ችለናል ብለዋል።

የሁለቱ ቤቶች የተሰራበት ዋጋ 1.2 ሚሊዮን ብር በገንዘብ ፣ በእውቀት እና በማቴርያል የፈጀ ሲሆን ይህንን ማህበራዊ ድጋፍ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

የከተማ ፣የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች ነዋሪዎች በተገኙበት የአቅመ ደካሞች ቤት የምርቃት መርሃ-ግብር ተከናውኗል።